ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያለኝን ሁለንተናዊ ግንኙነት ለማሳደግ ቁርጠኛ ነኝ አለች





ፊንፊኔ #Ethiopia መጋቢት 26,2015 (YMN) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በኢትዮጵያ ከጣሊያን አምባሳደር አጎስቲኖ ፓሌሴ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ኢትዮጵያ እና ጣሊያን ያላቸውን የሁለትዮሽ እና ዘርፈ ብዙ ግንኙነት ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡
አምባሳደር አጎስቲኖ ፓሌሴ ÷ ኢትዮጵያ ለቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ወሳኝ ሚና ያላት ሀገር መሆኗን አንስተዋል፡፡
የጣሊያን መንግስት ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ሁለንተናዊ ግንኙነት ይበልጥ ለማሳደግ ቁርጠኛ እንደሆነ ማረጋገጣቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

Post a Comment

0 Comments